Friday, July 25, 2008

ምዕራቡ ዓለምና የዴሞክራሲ ሬቶሪክ

ጌታቸው ረዳ

ከጥቂት ወራት በፊት በዚምባብዌ የተደረገውን ምርጫ ተከትሎ የምእራባውያን የዜና ማዕከላት ትኩረት በሮበርት ሙጋቤ እጣና በአፍሪካ አህጉር የዴሞክራሲ ሂደት ላይ አድርገዋል።የአፍሪካ ህብረት በሻረም አል ሼክ ተሰብስቦ በመከረበት ወቅት የዚምባቡዌና የሙጋቤ ጉዳይ ትልቅ አጀንዳ ነበረ።በጃፓን በተካሄደው የቡድን ስምንት ሀገራት ስብሰባ ላይም እንዲሁ ተመሳሳይ ጩኸት ተስተጋብቷል።በእኔ ዕምነት በጉዳዩ ላይ የምዕራቡ ዓለም መንግስታትም ሆኑ የመገናኛ ብዙሃን እያደረጉት ያሉት የተጠናከረ ዘመቻ የዚምባቡዌና የሙጋቤን ብቻ ሳይሆን አህጉሪቱ ለወደፊት የሚገጥሟትን ፈተናዎች ጭምር አመላካች ነው።ከላይ በጠቀስኳቸው ሁለት መድረኮች ላይ የአፍሪካ መሪዎች በሙጋቤ ላይ አሳዩት የተባለው ለስለስ ያለ አቋምም ይኸንን ፈተና በትክክል ከመገንዘብ የሚመነጭ ይመስለኛል።

ምዕራቡ ዓለምና የዴሞክራሲ ሬቶሪክ

እንግሊዛዊው ገጣሚ ራድያርድ ኪፕሊንግ በህይወት ዘመኑ ከሠራቸው የጥበብ ሥራዎች መካከል፡ ‘ዘ ዋይት ማንስ በርደን’ የሚል ርዕስ የሰጠው አሪፍ ግጥም ይገኝበታል።

Take up the White Man's burden--
Send forth the best ye breed--
Go bind your sons to exile
To serve your captives' need;
To wait in heavy harness,
On fluttered folk and wild--
Your new-caught, sullen peoples,
Half-devil and half-child.

By open speech and simple,
An hundred times made plain
To seek another's profit,
And work another's gain.


በየደረስክበት ሁሉ፣

እንጭጭ አንጎል ያላቸው ከጋኔን አብራክ ‘ሚከፈሉ፣

ከሰውነት ተራ የወጡ ወደ ዱር አውሬነት ያደሉ

በፍርሃት መረብ ተሸብበው ሰርክ በሽብር የሚኖሩ፣

አህዛብ ገብተዋል በእጅህ ያንተን ደግነት የሚሹ።

ዓለም በግልፅ ይወቀው

ራስህን ሳታስቀድም የአውሬዎቹን ጥቅም ብቻ አስበህ፣

በፅኑ ሰንሰለት ጠፍረህ ፣

ወደ መልካም መስክ ማሰማራት ያንተ እዳ መሆኑን አውቀህ፣

የስደትን አበሳ አስተምርና ምርጥ ልጆችህን አሰማራ፣

እንዲሸከሙ የነጮቹን ፈተና።

ኪፕሊንግ በዚህ ግጥም ምዕራቡ ዓለም ‘ያልሰለጠነውን’ ዓለም ከጨለማ የማውጣትን መለኮታዊ አደራ ጫንቃው ላይ እንደተሸከመ ዓለምን ሊያሳምን ሞክሯል።የታላቋ ብሪታንያ ቅኝ ግዛት የማስፋፋት ዘመቻ አካል እንደነበር ይነግረናል ባለቅኔው።

ዛሬ ከመቶ ዓመታት በሗላ ደግሞ፡ ናታን ሻራንስኪና ፍራንሲስ ፉኩያማን የመሳሰሉ የምዕራቡ ዓለም ሊቀ መኳሶች፡ ምዕራባውያን ‘ያልሰለጠነውን’ ዓለም በዴሞክራሲያዊነት ፀበል የማጥመቅ ታሪካዊ/‘መለኮታዊ’ ሃላፊነት እንዳለባቸው፤እንዲሁም መላው ዓለም ከዚህ ጥምቀት በተዓምር እንደማያመልጥ ቢገነዘበው እንደሚበጀው እየነገሩን ይገኛሉ።

በአፍሪካና በሌሎችም በልማት ወደ ሗላ የቀሩ ሀገራት ላይ የነበራቸው ተፅእኖ ለዘመናት ለማዝለቅ የቻሉት እንደየዓለማዊ ሁኔታው/እንደየአስፈላጊነቱ አካሄዳቸውንና ፍልስፍናዎቻቸውን በመቀያየር ነው። በቅኝ አገዛዝ ዘመናት ያለሃፍረት ዓይን ያወጣ ዘረፋ ላይ ተሰማርተው መዛቅ የቻሉትን ሁሉ ሲዝቁ ኖረዋል። ከነበራቸው የጠመንጃ የበላይነት በተጨማሪ የነራድያርድ ኪፕሊንግ ርዕየተ ዓለማዊ ድጋፍና የነአባ ማስያስ ወንጌላዊ መልዕክት ከፍተኛ ሚና ነበራቸው። ከ1960ዎቹ ወዲህ እስከ ቀዝቃዛው ጦርነት ማብቂያ ድረስ በእጅ አዙርና በአሻንጉሊት አስተዳዳሪዎች እየታገዙ መቀጠል ችለው አይተናል።ፒኖሼ፣ሱሃርቶ፣ሞቡቱ ናትሩሂዮን የመሣሠሉት ‘የብረት መዝጊያ’ የሆኑ ደንበኞች ስለነበሯቸው የሚፈልጉትን ሁሉ ከማግኘት የሚከለክላቸው አልነበረም። ከነዚህ መሪዎች ጋር ያደርጉት የነበረውን ‘ትብብር’ የሚያቀጣጥለው ሞተር ደግሞ ‘የኮሚኒዝምን መስፋፋትና የዶሚኖዎቹን ተከታትሎ መውደቅ’ ለማስቀረት ይደረግ የነበረው ዘመቻ ነበር።

የኮሚዩኒዝም ሥርዓት በዓለም አቀፍ ደረጃ ካከተመባቸው ከአስራ ዘጠኝ ሰማንያዎቹ የመጨረሻ ዓመታት ወዲህ ደግሞ፡ የመዋቅር ማስተካከያ ፕሮግራም(ሳፕ)፤ እንዲሁም የመልካም አስተዳደር ግንባታ አጀንዳን (ጉድ ጋቨርናንስ ዲስኮርስ) ለዘመናት የዘለቀውን የኒዮ ሊበራሊዝም ተፅእኖ ለእስከወዲያኛው ለማስቀጠል ሲባል ጥቅም ላይ የዋሉና በመዋል ላይ የሚገኙ ሥልቶች ናቸው። ከሁሉም ምዕራባውያን አንደበት የማይጠፋው መሪ ሃረግ(ካች ፍሬዝ) ግን “ዴሞክራሲን የማስፋፋት” ተልዕኮ ነው።

ዴሞክራሲያዊ ሥርዓት ገንብቷል ለመባል መድበለ ፓርቲ ሥርዓት፣‘ነፃ ምርጫ’፣ ፕራይቬታይዜሽን፣የንግድ ሊበራላይዜሽን፣ ‘ነፃ’ ፕሬስ፣የሲቪክ ማህበራት(መያዶች) ወዘተርፈ በአንድ ሀገር መሟላት ካለባቸው ግዴታዎች የተወሰነቱ ናቸው።ይኸ መሆኑ በርግጥ ባልከፋ።እንዳጋጣሚ ሆኖ የምንናገረው እጅግ በርካታ የተፈጥሮ ሃብት(ነዳጅ፣ወርቅ፣መዳብ) ስላለው ሀገር ከሆነ እላይ የጠቀስናቸው ተቋማት እምብዛም ላያስፈልጉ ይችላሉ።ጥያቄዎቹ እንዲሁ ለግብር ይውጣ ሊጠየቁ የሚችልበት እድል ግን ይኖራል።በኒዮ ሊበራል አጀንዳ አራማጅ ምዕራባውያን ዘንድ በአፍሪካ ሀገራት ውስጥ በሥልጣን ላይ ያሉ መንግስታት ዴሞክራሲያዊ ሽግግር አድርገዋል ሊባሉ የሚችሉት የተደረገው ምርጫ እነርሱ ትክክለኛ ነው ብለው ያቀረቡትን አካሄድ ብቻ ተከትሎ የተደረገ እንደሆነ ነው። ምርጫ የሚደረገው የነሱን ውቃቤ ለማስደሰት ሲባል ብቻ እንደሆነ ስለሚያምኑ አንድ አንድ ጊዜ አገሬው በነቂስ ወጥቶ ቢመርጥም ደስ ካላላቸው ዴሞክራሲያዊነቱን ባንድ መግለጫ ብቻ ሊሽሩት ይችላሉ።ለምሳሌ ኡጎ ቻቬዝ ወርዶ እስኪያዩት ድረስ ቬኔዝዋላ ውስጥ መቼም ዴሞክራሲ ተረጋግጧል የሚባል ጨዋታ ሊዋጥላቸው አይችልም።

ስልጣን በፉክክር ለመያዝ አስበው የሚንቀሳቀሱ ተቀናቃኝ ድርጅቶች ለዴሞክራሲ ግንባታ የማይተካ ሚና እንዳላቸው ብዙም ሙግት የሚያስፈልገው አይመስለኝም። የምዕራባውያኑ የዲሞክራሲ ተዋስኦ የሚያቀነቅነው የተቃዋሚ ፓርቲዎች ሚና ለራስ ሀገርና ህዝብ ሊኖር ከሚገባው ታላቅ ሃላፊነት የግድ መቆራኘት አይጠበቅበትም።ታዋቂ ሰው የሚመራውና ለትልቅ ለትንሹ አጋጣሚ ሁሉ ወደየ ሃብታም አገራት ኤምባሲ መሮጥ የሚቀናው ስብስብ ሁሉ አባላት መለመለም አልመለመለም የዲሞክራሲያዊ ሂደቱ አንደኛ ዘዋሪ ተደርጎ በየዕለቱ መሞካሸት ይጀምራል።አንዱን ጎሳ በሌላው ላይ አነሳስቶ ግርግር መፍጠር ከቻለየስልጣን መጋራትካልተደረገ ምፅዓት ይመጣል ብሎ የሚያስቸግር ዓይና አውጣ ሆኖ ያርፈዋል።ራሽያ ውስጥ ጋሪ ካስፓሮቭ የሚባል ዝነኛ ቼስ ተጫዋች የራሽያን ህዝብ ከመከራና ከነፑቲን አምባገነን አገዛዝ የማውጣት ተልዕኮ የያዘ ፓርቲ በማቋቋሙ ብቻ በምዕራባውያን ዘንድ እንደ ራሽያ የወደፊት ተስፋ ሊቆጠር በቅቷል።ለተራ አጀብ እንኳ የሚሆን የረባ ተከታይ አለማግኘቱ ለምዕራባውያኑ ምንም ማለት ላይሆን ይችላል። ደጋፊዎች አፈራም አላፈራም ካስፓሮቭ የራሽያ ዲሞክራሲ ተቀልብሷል ማለት መቻሉ ብቻ ይበቃል።ለነገሩ ምዕራባውያኑ ዓመል ሆኖባቸው ራሽያ ላይ ያፈጣሉንጂ አፍሪካ ውስጥ ያላቸውን ተፅዕኖ አንድ ሚልየንኛም ብትሆን ሊኖራቸው አይችልም።

የምዕራባውያኑ የዴሞከራሲ ሬቶሪክ ከተቃዋሚዎች ተሳትፎ አስፈላጊነት ጋር በተያያዘ ከቅርብ ዓመታት ወዲህ መግፋት የጀመሩትመፍትሄምአለ። የስልጣን መጋራት(ፓወር ሼሪንግ ዲል) ይባላል።የዚህ ሃሳብ ትክክለኘነት የሚመነጨው ምዕራባውያኑ ላላቸው ጥቅም ተገቢ ሆኖ ያገኙትን ሃሳብ ሁሉዲሞክራሲያዊነትለማላበስ ካላቸው መብት ብቻ ነው።ደጋፊዎቼ ተቆጥተዋልና ስልጣን ካልተጋራሁ ሞቼ እገኛለሁ!” የሚል አምታች ሁሉ የዴሞክራሲያ ሂደቱ መጠናከር ወሳኝ ሃይል ሆኖ ይወደሳል። እነሆ በዴሞክራሲያዊ መንገድ የፀደቀ ህገ መንግስት በዝርፊያ በተጣሉ ሁለት ወመኔ ፖለቲከኞች ፊርማ የሚሰረዝበትዲሞክራሲየምናይበት አስገራሚ ሰዓት ላይ ደርሰናል።

ኬንያን ለአብነት እንጥቀስ። ራይላ ኦዲንጋ በርካታ ደጋፊዎች መርጠውት ሊሆን ይችላል።ምርጫው ሊጭበረበርም ላይጭበረበርም ይችላል።ምዕራባውያኑ (ኮፊ አናን የድራማው መሪ መሆናቸው ለውጥ የለውም!) የኬንያውያንን የእርስ በርስ መተላለቅ ለማስቀረት በማሰብ የስልጣን መጋራት ሃሳብ መግፋት እስኪጀምሩ ድረስ የኦዲንጋ አቋም ምርጫው ስለተጭበረበረ መደገም አለበት የሚል ነበረ። በፀጥታ ሃይሎች የተገደሉ በሺዎች የሚቆጠሩ ሲቪሎች ጉዳይ ይጣራ እያለ ሲጮኽ ሰምተናል።ይሁንና በምዕራባውያኑምክርመሠረት ድሆች ወገኖቹ ዝር በማይሉበት የጎልፍ ሜዳ ውስጥ ተቀምጦ ደመኛ ጠላቱከኪባኪ ጋር ስልጣን ለመጋራት ከመስማማት አላገደውም።የሞቱት ካንድ ሺህ የሚበልጡ ሲቪሎች ጉዳይ ከዚያ በሗላ ማንሳት ለጠቅላይ ሚኒስትርነት ያበቃውንዲሞክራሲአደጋ ላይ ስለሚጥልበት የሚሞክረው አይሆንም። ይባስ ብሎ በዚምባብዌ ስለተካሄደው ምርጫ ከተሰጡት አስተያየቶች ሁሉ አስገራሚውን ውግዘት ያቀረበው/ሚኒስትርኦዲንጋ ነበር። ሰውየው ለሲኤንኤን የሰጠው አስተያየት ሙጋቤ ኢዝ ዲስግሬስ ፎር አፍሪካ!” የሚል ነበር።ኦዲንጋ የምሩን ይሁን የቀልዱን ለማወቅ ባይቻልም፡ አፍሪካ ህብረት በዚምባቡዌ ላይ ወታደራዊ ጣልቃ ገብነት መፈፀም እንደሚገባው ለማሳሰብ ጭምር ሞክሯል።

በምዕራባውያኑ ተዋስኦ መሠረት የዴሞክራሲያዊ ሥርዓትየግድ ከሚላቸውተቋማት ውስጥ መንግስታዊ ያልሆኑ ድርጅቶች(መያዶች) ያላቸው ሚና ትልቅ መሆኑ በምንም መልኩ ጥያቄ ውስጥ መግባት አይኖርበትም። የአገር በቀል መያዶች የህዝብን ዙርያ መለስ ፖለቲካዊ፣ኢኮኖሚያዊና ማህበራዊ ተሳትፎ በማነሳሳት ረገድ ያላቸው ሚና በፍፁም የሚካድ አይደለም። ነገርግን የድርጅቶቹ ተጠያቂነት ድርጎ ለሚሰፍሩላቸው ምዕራባውያንቀጭን ጌቶችብቻ በሆነበት እውነታ ውስጥ፡ የራሳቸውን ኢኮኖሚያዊና ፖለቲካዊ ተፅዕኖ በሌሎች ላይ ጥበብለመጫን የሚያስቡ ባዕዳን መጠቀሚአ የሚሆኑበት አጋጣሚ ይፈጠራል።በእንደዚህ ዓይነቱ ሁኔታ መያዶች ተጠያቂነታቸው እናገለግለዋለን ለሚሉት ሃገርና ህዝብ መሆኑ የሚቀርበት ሁኔታ(ኤክስተርናላይዜሽን ኦፍ አካውንቴቢሊቲ) ይፈጠራል።ሪታ አብራምሰንዲሲፕሊኒንግ ዴሞክራሲበሚል ርዕስ በሰጠችው መፅሃፏ ላይ በጉዳዩ ላይ ሰፊ ትንታኔን አቅርባለች። በእርግጥም ሪታ በትክክል እንዳስቀመጠችው፡ይኸው የመያዶች ገፅታ ከምንም ነገር በላይ አፍሪካ ውስጥ በተደጋጋሚ ለሚስተዋሉ የፖለቲካ ብጥብጦች በዋና እርሾነት ያገለገለበት ሁኔታ በተደጋጋሚ ተስተውሏል።

በምዕራባውያኑ የመልካም አስተዳደር ተዋስኦ መሠረት ማንኛውም አፍሪካ ውስጥ በግል ሚድያነትም ሆነ በመያድነት የተቋቋሙ አካላት ሁሉ በተፈጥሮአቸው ዴሞክራቲክ (ኢንኸረንትሊ ዴሞክራቲክ) ተደርገው የሚወሰዱበት ስነ ሞገት በበርካታዎቹ ሀገራት ማህበረ-ፖለቲካዊ መቼት ውስጥ ያለውን እውነታ በፍፁም ያገናዘበ አይደለም። ባንድ ሀገር ውስጥ ያሉ መያዶች አደረጃጀትም ሆነ እንቅስቃሴ የሚገዛበት ስነልቦናና አወቃቀር ዞሮ ዞሮ በሚፈጠሩበት ማህበረሰብም ሆነ ቡድን ውስጥ በስፋት የሚስተዋለውን እውነታ መከተሉ የማይቀር ነው። በመደብ የተከፋፈለ ማህበረሰብ ውስጥ የመደብ ወገንተኝነትን የሚያንፀባርቅ መያድ/ሚድያ በጎሳ ሽኩቻ ላይ የተመሰረተ የፖለቲካ ላዕላይ መዋቅር በሰፈነበት ህብረተሰብ ውስጥ ያንኑ የሚያንፀባርቅ መያድም ሆነ ሚድያ መኖራቸው ብዙም ጥናት የማይጠይቅ እውነታ ነው። ይሁን እንጂ ምዕራባውያኑ በደፈናው የሚነግሩን ተፈጥሮአዊዲሞክራሲያዊነት ከመጠርያነት በዘለለ በተግባር ላይ ሲውል አናይም። በስርቆት ላይ ብቻ እንደተሰማሩ የሚታወቁም እንኳ ቢሆን፡መንግስታዊ ያልሆኑ ድርጅቶች የዴሞክራሲያዊ ሥርዓት ዓይነተኛ መገለጫ በመሆናቸው ያሉትና ያረጉት ሁሉ በማንም ወገን ጥያቄ ውስጥ አይገባም። በሙስና ከሥልጣን የወረደ ሹመኛ በቀላሉ ሃጥያቱ እንዲሰረይለት ከፈለገ አቋራጩ መንገድ መያድ አቋቊሞስለ መልካም አስተዳደርልቡ ውልቅ እስኪል መታገል ብቻ ነው።

በምዕራቡ ዓለም ቡራኬ የማይገሠስ የሀቅ ሚዛንነት ሃላፊነትበ የተሰጣቸው ሌሎች ተቋማት ደግሞ የግል የመገናኛ ብዙሃን ናቸው። ጥላቻንና ሁከትን መስበክን ቋሚ አጀንዳቸው አድርገው የያዙትም እንኳ ቢሆኑ በምዕራባውያኑ መመዘኛ መሠረት የእውነት ሚዛኖች ሁነው መታየት አለባቸው። ጦርነት በመቀስቀሱና ከፍተኛ ወንጀል በመፈፀሙጋዜጠኛበህግ ቁጥጥር ስር የዋለ እንደሆነ፡ የዴሞክራሲ ሂደቱ እንደተቀለበሰ ሊቆጠር ይችላል። ባጭሩ የማተሚያ ቤት ወጪ ችሎነበልባል፣ማዕበል፣ቀረርቶ፣ሁከት…” የሚል ስም ጋዜጣውሰጥቶ የጭቃ ጅራፍ ሲያጮህ የሚውል ሁሉ ጋዜጠኛ ያሻውን የመፃፍመብቱየፕሬስ ነፃነት ህጉን ለማስከበር የተወሰደ ህጋዊ እርምጃ ደግሞ የፕሬስ ነፃነትን መዳፈር እንደሆነ በምዕራባውያኑ አስቀድሞ የተረጋገጠ ነው። ይኸን ዘመነኛ ቀኖና በትንሹም ቢሆን ለመፈተሽ የሞከረ መንግስትም ሆነ ሀገርከዴሞክራሲያዊ ሂደቱየማፈግፈግ አደገኛ ምልክት ተደርጎ ይወሰዳል።

እንደ ማጠቃለያ

ምዕራባውያኑ የዴሞክራሲ ስርዓት የማስፋፋት ተልዕኮአቸውን ለመወጣት የሚጠቀሙባቸው መንግስታዊ ያልሆኑ ምዕራባውያን ተቋማት አሏቸው። የእነዚህ ተቋማት ዓላማ በአንድ ሀገር ላይ ካለው ነባራዊ እውነታ በእጅጉ የተለየ ራሳቸውን የሚመች እውነታ መፍጠር ነው። ቢቢሲና ሲኤን ኤን፣ሁማን ራይትስ ዋችና ናሽናል ዴሞክራቲክ ኢኒስትትዩት ወዘተርፈ ሁሉ የሂደቱ ዋነኛ መሣርያዎች ናቸው።የኢኮኖሚያዊ ተፅኖ መፍጠር የፈለጉባቸው ሀገራት ውስጥ ደግሞ ከላይ ለመጥቀስ የሞከርካቸው ሃይሎች አማራጭ እውነታ በመፍጠር ይተባበራቸዋል፡፡ እንግዲህ ይህን ለጥቅማቸው መረጋገጥ ሲባል ለሚያደርጉት ጣልቃ ገብነት እንደ ግብዓት የሚያገለግል አማራጭ እውነታ የመፍጠርን ሂደት ነው ዴሞክራሲን የማስፋፋት ታሪካዊ ተልዕኮ በማለት የሚጠሩት፡፡

Saturday, July 19, 2008

Samuel Gebru, EAYI's Founding President, shall Confer with High-Ranking Government Officials, Opposition and Youth Organizations Leaders

Samuel Gebru, social entreprenuer and youth activist, is on official visit in Ethiopia. During his visit, he is expected to confer with various high-ranking government officials, opposition parliamentarians, youth leaders, businesspersons and religious leaders.

Samuel shall discuss matters pertaining to the enhanced cooperation and dialogue amongst youth organizations with the various youth leaders; issues relating to education, youth, diaspora, tourism and culture as well as economic and political development with the high-ranking government officials of the Federal and State governments of Ethiopia;

In a meeting with the religious leaders of Ethiopia, he shall focus upon creating and promoting interfaith dialogue, the history of faiths in Ethiopia, the Ethiopian Millennium celebrations as well as how they can be of support to the two delegations he will be heading in 2009, the Ethiopian American Millennium Delegation as well as the Ethiopian American Youth Initiative.

Furthermore, Samuel shall visit the following places during his stay in Ethiopia: the Addis Ababa University and the National Museum in ADDIS ABABA, the Mekelle University, Negash (Wukro), Semein National Park and Yeha in TIGRAY, the Bahir Dar University, Lalibela, and Bahar Dar (Lake Tana, Blue Nile Falls, etc.) in AMHARA, Adama and the Bale Goba National Park in Oromia, among others.

Finally, Samuel Gebru managed to blog successfully his first trip journal, covering July 12 - 17, 2008 from Mekele, the Capital City of the National Regional State of Tigray.

His trip journal can be accessed at the link below:
http://www.smgebru.blogspot.com/

Alemayehu Fentaw

Stadtschlaining, Austria


Monday, July 14, 2008

Ethiopians Are Proud To Be Black

As I was surfing on the world wide net, I just came across with an article on Time in its issue of Monday, 9th of January 1928. I was shocked and disgusted by the content of the article I read under the title "To Ethiopia". The gist of the article centers around a controversy as to why a certain Addison E. Southard, a white man from Kentucky, must be appointed to be a diplomat in the rank of a Minister to Ethiopia instead of a black man. I was shocked by the gross misunderstanding of the true identity of Ethiopians not only by the whites, but also by a few black colleagues whose acquaintance I have had in the few years I have spent with them both as a teacher and student. So I have taken it upon myself to tell the truth about our identity: that we Ethiopians are black and proud to be black; that we do not also need any patronization either from the whites nor from the blacks.

In an attempt to justify why a white man should be appointed to Ethiopia, the article says that "Despite their name, the Ethiopians do not consider themselves racially homogeneous with aboriginal Africa." It goes on to assert that "Color varies In Ethiopia, from a pale olive among the northern inhabitants, through deep brown in the central part of the Kingdom to chocolate tints and true black in the farthest south. Ras Taffari, prince regent, is a black southerner but of the special superior blackness of the province of Shoa. Slim, short, wiry, Prince Ras Taffari considers himself super-Negroid." This is totally a racist statement that does not portray the Ethiopian psyche/mentality as we know it.

A further explanation given in the same article is that "Prince Ras Taffari is of a turn of mind no less inquiring than Rasselas. He would...desire as envoy from any other state, a representative of that state's dominant race. Ras Taffari would want to learn about China from a Chinaman, not a white man; about India from a Hindu, not an Anglo-Saxon; about the U. S. from a Caucasian, not a Negro." This, for me, is uncharacteristic of neither the Ethiopian polity nor the crown prince, rather something typical of the American psyche at the time. If the US found it right not to send a black diplomat to Ethiopia, it was precisely because the US was a racist state adhering to racism and racial classification not only in its domestic public life but also in its international affairs.

Alemayehu Fentaw
Stadtschlaining, Austria

To read the Time article follow this link:
http://www.time.com/time/magazine/article/0,9171,881706,00.html?promoid=googlep

Samuel Gebru, the Founding President of EAYI, Visits Ethiopia

Samuel Gebru, the Founding President of the Ethiopian American Youth Initiative, is on official visit to Ethiopia. The Ethiopian American Youth Initiative is known for its assistance to the Fistula Hospital, Famine Relief, and Abebech Gubena in Ethiopia. Samuel Gebru is an exceptionally talented young Ethiopian American from Boston area. He flew the Ethiopian Airlines, ET501, from Dulles International Airport and arrived in Addis Ababa Bole International Airport on Sunday, 13th of July 2008 at 7 PM.

According to my sources, he will stay in Ethiopia until 24th of August, 2008. During his stay, he will undertake fact-finding and participant-observation regarding social, political, and economic problems facing the Ethiopian polity. Besides, he will forward questions he collected from various Ethiopians through his site to concerned high-ranking government officials.

If you want to know more about the activities of his organization you can visit this site: www. ethusa.org. In addition, he has got his own blogsite: www.smgebru.blogspot.com.

Tuesday, July 8, 2008

Samuel Gebru will pay visit to Ethiopia

Samuel Gebru, an exceptionally talented young Ethiopian American from Boston area, will be on official visit to Ethiopia. He is the founder and president of EAYI( the Ethiopian American Youth Initiative), which is known for its assistance to the Fistula Hospital, Famine Relief, and Abebech Gubena in Ethiopia. If you want to know more about the activities of his organization you can visit this site: www. ethusa.org. In addition, he has got his own blogsite: www.smgebru.blogspot.com. He will be on Ethiopian Airlines flight ET501 from Dulles International Airport which arrives in Addis Ababa Bole International Airport on Sunday, 13th of July 2008 at 7 PM.

Wednesday, July 2, 2008

አንዳንድ ነጥቦች ስለተቃውሞው ወገን


በጌታቸው ረዳ

ከጥቂት ሳምንታት በፊት በአዲስ ነገር ጋዜጣ ላይ ሀገራችን ውስጥ ያሉ ተቃዋሚዎችን በሚመለከት የግሌን አስተያየት የሚገልፅ አንድ ፅሁፍ አቅርቤ ነበር።የነ አቶ አንዳርጋቸው ፅጌን ‘አዲሱ የትግል ስትራተጂ’ እንደ መነሻ በመውሰድ የሀገራችን ተቃዋሚዎች ብዙም ሊበረክቱ ያልቻሉባቸውን መሠረታዊ ችግሮች ናቸው ያልኳቸውን የተወሰኑ ትዝብቶች ለማቅረብ ሞክሬ ነበር።በእኔ ግምት እንደዚህ ዓይነቱ ፅሁፍ ድርጅቶቹን በሚመለከት በስፋት የሚስተዋለውን በረባ ትንታኔ ላይ ያልተመሠረተ ድጋፍም ይሁን ተቃውሞን በቅጡ ለመፈተሽ የሚያስችል መጠነኛ አስተዋፅኦ ሊያደርግ ይችላል ብየ አስቤ ነበር።ይሁንና አሁንም ቢሆን በጉዳዩ ላይ ስር የሰደደ የግንዛቤ ችግር ያለባቸው ሰዎች እንዳሉ በትክክል ተረድቻለሁ። የፅሁፉ ዓላማ የተዳከሙ ድርጅቶች ጨርሶ ለማጥፋት የተሸረበ ሴራ ተደርጎ ተወስዶ ከሆነ ደግሞ፡ ዞሮ ዞሮ ተጠያቂው ተቃውሞ በፍፁም የማይፈቅደው የተቃውሞ ባህላችን እንደሆነ ሊሰመርበት ይገባል።ስለዚህ የአንዳንድ ሰዎችን ብዥታ በመጠኑም ቢሆን ያቃልል እንደሆን በማለት በርዕሱ ላይ የአሉኝን አስተያየቶች በዛሬው ፅሁፌም ዘርዘር አድርጌ ለማቅረብ እሞክራለሁ።

ባለፈው ፅሁፌ ለማስቀመጥ እንደሞከርኩት በርካቶቹ የሀገራችን ተቃዋሚ ድርጅቶች የሚስተዋሉባቸው እጅግ ብዙ ድክሞቶች ቢኖሩም በዛሬው ፅሁፌ በአራት ዋና ዋና ድክመቶቻቸው ላይ አተኩራለሁ።

የሀገራችን ተቃዋሚ ድርጅቶች አንዱ መሠረታዊ ችግር ወደ ተቀናቃኝ ድርጅትነት ማደግ አለመቻላቸው ነው። የሁለቱን ልዩነት በመጠኑም ቢሆን ላብራራ።ባለፈው ፅሁፌ ለመጥቀስ እንደሞከርኩት በአንድ ሀገር የፖለቲካ መድረክ ውስጥ ተሳትፎ ለማድረግ የተቋቋሙ ድርጅቶች የሚንቀሳቀሱት ዲበአካላዊ(ሜታፊዚካል) ለሆነ ዓላማ አይደለም።ቢያንስ ቢያንስ ተቀናቃኝ ድርጅቶች የሚታገሉት ለሥልጣን ነው። ፓርቲዎች ዓለማቸው የፖለቲካ ሥልጣንን ህግ በሚፈቅደው አግባብ ለመያዝ እስከሆነ ድረስ ትግላቸው የዴሞክራሲያዊ ሥርዓት ወሳኝ መገለጫ መሆኑ እሙን ነው።ለዚህም ሲባል ተቀናቃኝ ድርጅቶች፡

  • በተለያዩ ያገሪቱ ክልሎች በሚኖሩ ህዝቦች ውስጥ በየደረጃው ዘልቀው በመግባት አባላትና ደጋፊዎችን ለማፍራት ይሠራሉ፤አባላት የሚመለምሉበትም መሥፈርት በግልፅ ያስቀምጣሉ።
  • ለዓላማዎቻቸው መሳካት ሲባል ይጠቅማሉ ያሏቸውን ግልፅ ስትራተጂዎችንና አቅጣጫዎችን በመተለም፡አስፈላጊውን ቁሳዊ፣ፖለቲካዊና ህሊናዊ ዝግጅት ያደርጋሉ።
  • ይነስም ይብዛም ከገዥው ፓርቲም ሆነ ከሌሎች ተቀናቃኞች የሚለያቸውን የአጭርና የረዥም ጊዜ ፕሮግራማ ቀርፀው ይንቀሳቀሳሉ።
  • ምርጫ ተቃረበም አልተቃረበም ሀሳቦቻቸው ሰፊ ተቀባይነት እንዲያገኙ የሚያስችሏቸውን የቅስቀሳ ሥራዎችን ይሠራሉ።
  • የዲሞክራሲ ግንባታ ሂደት ረዥም ጊዜን የሚወስድና የሁሉም ህዝቦች ዙርያ መለስ ተሳትፎ እንደሚጠይቅ በማመን ለመተማመን ባህል መጎልበት የሚቻላቸውን ሁሉ ይሠራሉ።
  • ‘የመንግሥት ሥልጣን አሁንና እዚችው!’ በማለት አገር ይያዝልን አይሉም፤ ወዘተርፈ።

በአንፃሩ ደግሞ ባገራችን ውስጥ እስካሁን ተመስርተው ያየናቸው ድርጅቶች፣ ህብረቶች፣ቅንጅቶችና መድረኮች እንዳለመታደል ሆኖ እዚህ ግባ የሚባል የተቀናቃኝነት ቁመና ኖሯቸው ለማየት አልታደልንም።ሁሉም ማለት ይቻላል አገራችን ውስጥ ያሉት ድርጅቶች ተቃዋሚዎች ብቻ ናቸው።

ተቃዋሚ ድርጅቶች ከተቀናቃኞች የሚለዩት፤

  • ልማድ ሆኖባቸው በዘፈቀደ ከሚጠሩት ግዙፍ ቁጥር በስተቀር በቅጡ የመዘገቧቸው ለቁጥር የሚገቡ አባላት የሏቸውም።
  • አባሉት አፈራን ባሉበት ወቅት እንኳ በግልፅ የሚታወቅ የምልመላ መሥፈርት በፍፁም አይኖራቸውም። ‘የሁሉም የኢትዮጵያ ህዝብ ይሁንታ’ አግኝተናል ብለው ስለሚያምኑ ‘ሁሉም ኢትዮጵያዊ አባላችን ነው!’ የሚል አስቸጋሪ ምላሽ ይቀናቸዋል።
  • ቀለል ባለ ምድራዊ ቋንቋ የሚገለፅ ለይስሙላም ቢሆን የተቀመጠ ፕሮግራም የላቸውም።
  • በተለያዩ ሀገራዊ ጉዳዮች ላይ ያሏቸውን በትንታኔ ላይ የተመሠረቱ ዝርዝር አቋሞችን ከመያዝ ይልቅ በተገኘው አጋጣሚ ሁሉ ጥቅል መፈክሮችን ማሰማትን ይመርጣሉ።
  • የትግላቸው ዓላማ ‘ገዢውን ፓርቲ በመገርሰስ መሪዎቹን ለፍርድ ማቅረብ’ እንደሆነ ስለሚያውጁ ወዳጅ ተጠላት ሁሉንም ያስበረግጋሉ።
  • በየእንጀራቸው ተሠማርተው ይከርሙና “ገዢው ፓርቲ በሩን ገርበብ እንዳረገው” በመገንዘብ በምርጫ ሰሞን በመሰባሰብ “በርግደው ለመግባት” ለሥልጣን ያበቃናል ያሉትን ያለ የሌለ መንገድ ለመጠቀም ይሞክራሉ።
  • ባጭሩ በተቃውሞ ተወልደው፤ በተቃውሞ ጀንበር ታዘቀዝቅባቸዋለች።

ያገራችን ተቃዋሚ ድርጅቶች ሌላው ችግር፡ በተናጠል የሚደራጁበትም ሆነ ከሌሎች ድርጅቶች ጋር ህብረት የሚፈጥሩበት በይፋ የሚታወቅ ንዑስ ፕሮግራም ኖራቸው የማያውቅ መሆኑ ነው። ምናልባትም ደግሞ ያስፈልገናል ብለው አያምኑም።በርካታ ትብብሮች አስራ ምናምን ጊዜ ተቋቁመው፣ አስራ ምናምን ጊዜ ፈርሰው ሲያበቁ፡ እንደገና ባዲስ መልክ በሌላ ዙር ዘመቻ ለማገገምና እግር ለመትከል ሲራኮቱ፡ ለጉድ ጎልቶን እያየናቸው አልፈዋል። በርካታ ያልተሳኩ ጥረቶችና ያልተጨበጡ ህልሞች እያየን እዚህ ደርሰናል። ይህን መሠሉ የተቃዋሚዎቻችን የማያቋርጥ የዘወትር ሽክርክሪት በማያሻማ መልኩ የሚነግረን ከላይ የጠቀስኩትን ይኸን አሳዛኝ እውነታ ነው። ከ1984 ዓ.ም. ወዲህ ባገራችን የፖለቲካ መድረክ ተፈጥረው ለረባ ፍሬ ሳይበቁ የከሠሙ ስንት አማራጭ ምክርቤቶች፣ስንት ህብረቶች፣ስንት ቅንጅቶችና ስንት መድረኮችን እንደታደምን ቤቱ ብቻ ይቁጠረው።

የፕሮፌሰር በየነ አማራጭ ሃይሎች ምክርቤት/ኢዴሃቅ/ህብረት( አሁን ደግሞ መድረክ!) ውስጥ ተካተው የነበሩትም ሆነ አሁንም ድረስ ያሉት ‘ሃይሎች’ ያላቸውን ለእስከወዲያኛው የማይታረቅ ጠላትነት ላወቀ፡ ምን ንዑስ ፖለቲካዊ ፕሮግራም አንድ ላይ እንዳሰባሰባቸው ለመረዳት ራሱን የቻለ ሳይንስ ሳይጠይቅ አይቀርም።ኢህአፓና መኢሦን፣ ኢዲዩና ዓረና ትግራይ፣ አቶ ስየ አብርሃና ቀኛዝማች ነቅዓ ጥበብ፣ ዶ/ር ነጋሶና ኢንጅነር ቅጣው እጅጉ ወዘተርፈ፤ ሊጋሩት የሚችሉትና ‘ፅኑ የትግል ጓዶች’ ለመሆን የሚያበቃቸው የፖለቲካ አቋም ምን እንደሆነ እርግጠኛ ሆኖ መናገር የሚቻል አይመስለኝም።

ሌላውን ሁሉ ትተን ከአሥራ ስንት ዓመታት በሗላ እንደ መዳፋችን አብጠርጥረን የምናውቃቸው የሚመስሉን ፕ/ር በየነና ዶ/ር መረራን ለምሣሌ እንውሰድ።ህብረታቸው ወይም አዲሱ መድረክ በሆነ አጋጣሚ የፖለቲካ ሥልጣን ለመቆናጠጥ በቃ እንበል። የዶ/ር መረራ ጉዲና ኦብኮ/ኦህኮ “ለምለሙ የኦሮሚያ መሬት ተመልሦ በነፍጠኛው እጅ እንዳይገባ” ሲባል በመንግሥት እጅ መሆን እንዳለበት በፅኑ ያምናል። የፕ/ር በየነ የሀዲያ ህዝብ ግንባር/ደቡብ ህብረት/ኢሶዴፓ በበኩሉ፡ “የገበያ ህግ በሚደነግገው መሠረት መሬት መሸጥ መለወጥ” እንዳለበት አጥብቆ ይሟገታል። ልዩነትን ተቀብሎ የመሄድ ባህል በሌለበት ሀገር እንዲህ ዓይነቱ አጋጣሚ አዎንታዊ ሊመስል ይችል ይሆናል። የ ‘መቻቻላቸው’ ምክንያት ግን በዴሞክራሲያዊ ሥርዓት ውስጥ እንዲኖር ከምንመኘው የመቻቻል ባህል ጋር ያለው ቁርኝት እጅግ አነስተኛ እንደሆነ ብዙም ነቃሽ የሚያሻው አይመስለኝም።

ዶ/ር ብርሃኑና ኢ/ር ሃይሉ ሻውል የቀድሞ ድርጅታቸው ቅንጅት የሚከተለውን ርዕዮተ ዓለም በሚመለከት ከእውነትነት ይልቅ ወደተረትነት የቀረበ ልግሥና ነበራቸው። ‘ሊበራል ዴሞክራሲ’ ምን እንደሆነ ሊያብራሩልን ብዙም ግድ ያልነበራቸው ቢሆንም፡ ሃይማኖታቸው እስኪመስለን ድረስ በተገኘው መድረክ ሁሉ ሲሰብኩልን ነበረ።በወቅቱ ለጋዜጦች ይሰጧቸው ከነበሩት ቃለ መጠይቆች በተደጋጋሚ ለመረዳት እንደቻልነው፡ ቅንጅታቸው በርካታ ሥራዎችን የመሥራት እቅድ ነበረው። በወቅቱ በተነገረው መሠረት በአዲስ አበባ ከተማ ውስጥ በሁሉም አቅጣጫ የሚዘረጋ የህዝብ ማመለላሻ ባቡር አገልግሎት መጀመር ከዕቅዶቻቸው አንዱ እንደነበር ሰምተናል።በወቅቱ ግን ከመሪዎቹም ሆነ ከደጋፊዎቻቸው መሃል ‘የባቡሩ ፕሮጀክት’ በባህሪው ወደሶሻሊስትነት በጣም የሚያደላ ከመሆኑ የተነሳ አብዮታዊ ዴሞክራሲ እንኳ እስከዚህም ደፍሮ የማይገባበት እንደሆነ የጠቆመ አልነበረም።

የፕ/ር መስፍን ‘ሶሻሊስት ዴሞክራትነት’ ከኢንጅነር ሃይሉ ‘ሊበራል ዴሞክራሲ’ ይልቅ፡ ‘ያገዛዝ ሥርዓቱ’ ለሚከተለው አብዮታዊ ዴሞክራሲ የተሻለ ቅርበት አለው ብሎ መሞገት ይቻላል።ዶ/ር ብርሃኑ በ ‘አዲሱ ስትራተጂያቸው በሁለ-ገብ ትግል ሊገረሥሱት’ የተነሡት ‘የአቶ መለሥን የጎሳ ፖለቲካ’ እንደሆነ ቋቅ እስኪለን እየሰማን ነው። ይሁንና ይኸኛው አቋማቸው ኢትዮጵያን ‘በጎሳ ለመገነጣጠል’ ነፍጥ ካነገቡ ነውጠኞች ጋር ቺርስ ከመባባል ፈፅሞ ሊያግዳቸው አይችልም። አቶ ገብሩ አስራት ወደ ‘ዴሞክራሲያውያን ሃይሎች’ ጎራ ለመቀላቀል፡ዝርዝር አቋማቸውን ማሳወቅ አላስፈለጋቸውም፡፡ ላለፈ ጥፋታቸው (በአሰብ ጉዳይ?!) ባደባባይ ይቅርታ መጠየቅ መቻላቸው ብቻ በቂ ነበረ።(ምንም እንኳ በብዙዎች ዘንድ ያለፈ የትግል ታሪካቸውን ሙሉ በሙሉ እንደባከነ መቁጠራቸው ባይወደድላቸውም!)

በቅርቡ እንደሰማነው ደግሞ አቶ ስየ አብርሃ ከ ‘ዕብሪተኛ የወያኔ መሪዎች’ ዝርዝር ወጥተው ባጭር ጊዜ ውስጥ ወደ ለውጥ አራማጅነትና ‘በሳል ፖለቲከኝነት’ ጎራ መመደብ የቻሉበት አስገራሚ ሽግግር እንዳደረጉ ተነግሮናል።ማንኛችንም ለማየት እንደቻልነው የአቶ ‘ሽግግር’ ረዘም ያለ የሃሳብ ልውውጥም ሆነ መሠረታዊ የጋራ ፖለቲካዊ አቋም ለመፍጠር የሚያስችል መድረክ የጠየቀ አልነበረም። የተቃውሞውን ጎራ ለመቀላቀል የሚያስፈልገው ብቸኛ የይለፍ ቃል፡ “የመለሥ አምባገነን አገዛዝ ላለፉት አሥራ ሰባት ዓመታት” የፈፀማቸውን ተግባራት ዓይንን ሳያሹ መኮነን ብቻ ነው።

ዝርዝሩን ገልፀን የምንጨርሰው ስለማይሆን በዚሁ እንለፈውና፡ የአንድ ሚልየኑን ብር ጥያቄ እናንሳ። እነዚህ ሁሉ ህልቆ መሣፍርት የሌላቸው ባተሌ ተቃዋሚዎች ባንድ ቅንጅት፣ባንድ ህብረትም ሆነ ባንድ መድረክ ለመሰባሰብ ያበቃቸው የሚታወቅ የጋራ መስመር ወይም ርዕዮት በእርግጥ አላቸውን?! ከግራም መጡ ከቀኝ ተቃዋሚዎቻችንን አንድ ላይ እንዲያብሩ የሚያደርጋቸው የጋራ ፕሮግራምም ሆነ የሚታወቅ መርህ-ተከል ርዕዮት የላቸውም፤ ወይም ደግሞ በፍፁም አያስፈልጋቸውም። ሃገራችን ለገጠሟትም ሆነ ወደፊት ለሚገጥሟት ችግሮች ምክንያቱም ሆነ መንስዔው አቶ መለሥ መሆናቸውን መቀበል ብቻ በቂ ነው። ይኸ ደግሞ መቀባባቱን ትተን በትክክለኛ ሥሙ እንጥራው ከተባለ ንፁህ ጥላቻ ብቻ ነው። ከዚህ መሰሉ የጋራ ጥላቻ ውጭ እስካሁን ያየናቸው ህብረቶች፣ቅንጅቶች፣አንድነቶችም ሆኑ መድረኮች፡ ተቻችለው ለአንዲት ጀንበርም ብትሆን መዝለቅ ቢችሉ እንኳ ራሱን የቻለ ተዓምር ነው!

የተቃዋሚዎች ሌላው ችግር ምድራዊ መመዘኛ በሌላቸው ሰማያዊ ፅንሰ ሃሳቦች ተጠፍረው የሚንከላወሱ መሆናቸው ነው።ዓላማዎቻችን የሚሏቸው ነገሮች ከሚጨበጡ ግቦች ይልቅ ዲበአካላዊ ቅኝት(ሜታፊዚካል ሪዞናንስ) ያመዘነባቸው ፅንሠ ሃሳቦችን መጥቀስ ያበዛሉ።የመደራጀታቸውን ወይም በህብረት የመቀጠላቸውን አስፈላጊነት በተመለከተ የሚሰጧቸው ብዙዎቹ ገለፃዎች የባህታውያንና የነቢያት ብቻ ይመስሉን በነበሩ አስፈሪ ቃላትና ሃረጎች የሚሞሉበት ጊዜ ያመዝናል። የሚቋቋሙበትም ሆነ ከሌሎች ጋር ህብረት ለመፍጠር የሚያስቡበት ምክንያት፡ከዕለት ተዕለት ፖለቲካዊ አጀንዳዎች ጋር ከማስተሣሰር ይልቅ፡ “ትውልድን ከእልቂትና ከመከራ ማዳን” በሚሉና በሌሎች መሠል ቋንቋዎች የሚገለፅ ‘መሢሃዊ’ ተልዕኮ ማነገብን ይመርጣሉ። የምፅአት ወሬና የአርማጌዲዮን መቃረብ ዜና ካላከሉበት ህብረታቸው የሚሰነብት አይመሥላቸውም። “ይህች አገር የገባችበት የጥፋት ማጥ፣ ወደ ገደል የሚገባው ባቡር፣ የጎሳዎች የእርስ በርስ መባላት” ወዘተ ብለው ካላስፈራሩን ተቃውሟቸው ድምቀት የማይኖው ይመሥል በስምንተኛው ሺህ ወሬ ያዋክቡናል።

ከተቋቋመ ጀምሮ የርስበርስ ጭቅጭቅ ተለየቶት የማያውቅ፣ አለመተማመን የነገሠበት፣ ወዴት መሄድ እንዳለባቸው በቅጡ በማያውቁ አመራሮቹ አለመግባባት ህልውናው ቋፍ ላይ የደረሰን ድርጅት እንዴት ሦስት ዓመት ሙሉ ሥራ አስፈትቶን እንደከረመ የምንስተው አይመሥለኝም። መሬት ላይ የቆመ እግር ያልተከለን ድርጅት ‘ቅንጅት መንፈስ ነው!’ የሚል ሰማያዊ ተልዕኮ አሸክሞ (ቀድሞውኑም ባልነበረው አቅም!) ከተፈጥሮአዊ ዕድሜው በላይ እንዲቀጥል የተደረገው ከንቱ ልፋት የትም ሊደርስ ያልቻለውም ለዚህ ነው።ባመራሩ ውስጥ አለመግባባት ሲፈጠርም ሆነ ከውስጥ ድክመት የመነጨ ከበድ ያለ የህልውና ፈተና ሲገጥም፡ ቀበቶን አጥብቆ በውይይትና በአመራር ብቃት፤ ወይም በህዝብ አመኔታ ላይ በመመሥረት መፍትሄ መሻት ብዙም አይታሰብም። ይልቁንም “የኢትዮጵያ ህዝብ ተዓምር መፍጠር አያቅተውም፤ አንዳች ተዓምር ተፈጥሮም ቢሆን” ወዘተርፈ ወደሚሉ መጨበጫ የሌላቸው ኢ-ፖለቲካዊ (መንፈሳዊ) ማፅናኛዎች መጠጋትን ይመርጣሉ።

ተቃዋሚዎቻችን የተጠናወታቸው ሰማያዊነትን/መለኮትን የሚታከክ አባዜ፡ ራሳቸውን የድርጅት ጥንካሬ፣የዓላማ ፅናት፣የመስመር ጥራት ወዘተ በመሳሰሉት የሚታዩ መሥፈርቶች በመመዘንና በመፈተሽ አካሄድን ለመቃኘት ከመሞከር ይልቅ፡ ጊዜን በጉንጭ አልፋ ክርክር እንዲያሳልፉ ዳርጓቸው አስተውለናል።አሁን አሁን ‘ቅንጅት’ን ያቋቋሙት ሃይሎች ወደ አሥራ ምናምን ትንንሽ ተበታትነው እያለ ጭምር፡ “የመንፈሱ ወራሾች እኛ ነን” የሚል አስቂኝ ሙግት ውስጥ ገብተው የምናየውም ለዚህ ነው። መፍትሄው ከሰማያዊ ይልቅ ምድራዊነቱ ወዳመዘነ የተቀናቃኞች ፖለቲካ ውለው ሳያድሩ መመለስ መቻል ነው።

በመጨረሻ ላነሳው የምፈልገው የተቃዋሚዎቻችን ድክመት ደግሞ ባለፈው ፅሁፌ ማጠቃላያ ላይ ላነሳው የሞከርኩት ነጥብ ነው። አሁንም ቢሆን የብዙዎቹ ችግር አዲሲቷን ኢትዮጵያ ፈፅሞ የማያውቁ መሆናቸው፤ ወይም ደግሞ ለማወቅ አለመዘጋጀታቸው ነው። ይኸንን እውነታ ከማንም በላይ ፕ/ር መስፍን ወልደማርያም ባንድ ወቅት ‘ርዕይ 2020’ በተባለ መድረክ ላይ በ1996 ዓ.ም. ባቀረቡትን ፅሁፍ በትክክል አስቀምጠውት እንደነበር አስታውሳለሁ። አቶ ደሳለኝ ራህመቶ የዮሃንስ ራዕይ ጥላ ያጠላበት(አፖካሊፕቲክ) ይመሥላል በሚል በገለፁት በዚህ ፅሁፍ ውስጥ በርካታ ጉዳዮችን ተነስተዋል። ፕ/ሩ በኢህአዴግ ‘ያገዛዝ ሥርዓት’ ፖሊሲዎች አማካይነት ኢትዮጵያ የጥፋት ገደል አፋፍ ላይ እንደደረሰች ይገልፃሉ።አገሪቱ ከጥፋት የምትድንበት ብቸኛ ዕድል ኢህአዴግ በቀጣዩ ዓመት(ምርጫ 97!) ለተቃዋሚዎች ሥልጣኑን አሳልፎ የሰጠ እንደሆነም ተንብየው ነበር። እንደሳቸው እምነት “የሚያውቋት ኢትዮጵያ ከመሠረቷ እንደተናደች” ና ይደርሳል ብለው የተነበዩት የመጨረሻ ምዕራፍ በ1997 ክረምት ላይ እንደሚገባ ባፅንኦት ሞግተዋል። 97 ክረምትን ለምን የመጨረሻው ምዕራፍ መባቻ መሆኑን የገለፁበት ዋነኛው ምክንያት በኢህአዴግ “መርዛም አስተሳሰብ ተኮትኩቶ ያደገው” ያሉት ትውልድ ፖለቲካ ውስጥ መግባት የሚጀምርበት ጊዜ በመሆኑ እንደሆነ ይጠቁማል ፅሁፋቸው።

አዲሲቷ ኢትዮጵያ ፕሮፌሰር መስፍን የሚያውቋት “ከመሠረቷ የተናደችው”ን ኢትዮጵያ የተካችዋ ኢትዮጵያ ስትሆን፤የአዲሲቷ ኢትዮጵያ አዲሶቹ ዜጎች ደግሞ ፕ/ሩ የጥፋት ወኪሎች እንደሚሆኑ የገመቷቸው ከኢትዮጵያ ህዝብ ቁጥር ከ70% የማያንስ ቁጥር ያላቸው ወጣቶች ናቸው። ተቃዋሚዎች ይኸን እውነታ ለመቀበል ካልደፈሩ የፖለቲካው ዓለም ዳይኖሰሮች ሆነው የሚቀሩበት ዕድል እጅግ ከፍተኛ ነው።